Search This Blog

Saturday, October 15, 2011

ሲሾም የበላ ሲሻር ያጥወለውለዋል

ሲሾም 
 
እነ ዋጥ-ሰልቅጤ እነ አግበስብስ መጥምጤን የሚያበረታታውን አባባል ታውቁታላችሁ:: "ሲሾም ያልበላ ሲሻር ይቆጨዋል::" እኔ ግን ሲሾሙ የሚያግበሰብሱና እና የሚሰለቅጡ በኋላ ቃር እንዳይሆንባቸው መጨነቅ ያለባቸው ይመስለኛል:: ታሪክም ደግሞ በሩቅም በቅርብም በስልጣን ላይ እያሉ ያለመጠን እየሰረቁ የጎሰጎሱት የግፍ እንጀራ በትግል ወይ በጊዜ ከወንበር ላይ ሲሽቀነጠሩ እንዴት እንዳቅለሸለሻቸው አሳይታናለች:: አንዳንዶች በንጹሐን ደም እየታጠቡ የተጨመላለቁ ነገስታትም የጊዜ አምላክ አሳልፎ ሲሰጣቸውና ድንገት ከከፍታቸው ሲፈጠፈጡ ደማቸው ደመ ከልብ ሁኖ መፍሰሱን ሰምተናል:: እናም ዛሬ ተገኘ ብሎ ናላ እስኪዞር ከርስ እስኪወጠር መሰርጎድ ምናልባት በኋላ ላይ ለትውከት እና ለሸርተቴ ሊዳርግ ይችላልና ተሿሚዎች የሆንን ሁሉ(እንዳንዶቻችን በራሳችን ላይና በቤት' እንዳዶቻችን በቤተ-ክርስቲያን' አንዳንዶቻችን በአገር ላይ…..ወ.ዘ.ተ.. ተሹመን ይሆናል) በመጠን ብንበላ!!
//--//
መስከረም 3 2004 ዓ.ም
እኩለ ለሊት
ሳር

Friday, October 14, 2011

አንዳንድ ጊዜ አለ አይደል??

አንዳንድ ጊዘ አለኮ......በጠራራና አድርቅ ፀሐይ በቁር የምንኮራመትበት:: አንዳንድ ጊዜ አለ አይደል?? አምላክ ከትንፋሻችን ይልቅ ተጠጋግቶን በትንፋሹ እያሞቀን ግን በናፍቆቱ የምንሰቃይበት!! አንዳንድ ወቅት እኮ አለ........ጓደኞቻችን በዙሪያችን ተኮልኩለው እየወደዱን በወሪያቸው እየጠመዱን ግን በብቸኝነት የምንነፍዝበት:: አንዳን ጊዜ እኮ አለ.......አምላካችን ከ አንዳንድ ጊዜ ወደ ዘላለም ዘላለም እስኪወስደን ድረስ::