Search This Blog

Thursday, June 30, 2011

ሰው ሳይጠራ ትምህርት ይጠራል?


ቅርብ ጊዜ ሪፖርተር ጋዜጣ ላይ በኢትዮጵያ ስላለው የትምህርት ጥራት ችግር የሚያወራ መጣጥፍ አነበብኩ:: ለመጣጥፉ እንደ ምላሽ የተሰጡት አስተያየቶች እያንዳንዳቸው የሰጡት ምላሽ ላይ የወቀሱት አካል ወይ የነቀሱት አሰራር አለ::

በግልፅ ልንረዳው እንደምንችለው የትምህርት ጥራት ጉድለት ችግር ምንጩ አንድ ነው በሎ ማቀንቀን ሞኝነት ነው:: ምናልባት ችግሩ ላይ የሁላችንም እጅ አለበት:: ያልተነሳሳና ንፋስን መከተል በሆነ ፍልስፍና የታሰረ ትውልድና ትጋት የሌለው ማንነነት ለውጥ የማምጣት አቅም ያንሰዋል:: የትምህርት ዋንኛ አላማ ገንዘብ ማግኝት በሆነበትና ተማሪዎችና መመህራን ገንዘብ ለማግኘት የእውቀትን ጥማት አፈር ድሜ ሊያስግጡና ለወረቀት ብቻ ሊሮጡ በሚያሰፈስፉበት ድንዛዜ ውስጥ አለን::

እሺ ተጠያቂው መንግስት ነው እንበል:: መንግስት ማነው? የህዝብ የአንተ የኔ በውሸት የሚያስመርቀው ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎችና መምህራን ስብስብ አይደለም::የኮምፒውተር መሸመቻና የ አይ ቲ ማስፋፊያውን ገንዘብ መጨፈሪያ የሚያደርገው አጎትህ አክስትህ ወይ ጎረቤትህ አይደለም?
ፍትህ ከቤት ይጀምራል:: ሰው በየራሱ ሲለውጥ ብዙ ሰዎች ይለወጣሉ:: በርግጥ አስተዳደር ላይ የተቀመጡ ሰዎች ሊያደርጉት የሚችሉትን አስተዋጽኦ መናቅ አይቻልም:: ግን ችግሩ በነዚህ አካላት ብቻ የተፈጠረ ነው ማለት እውነታውን መካድ ነው::
መምህራንም ተማሪዎችም( አብዛኞቹ) ለመማርና ለማስተማር መነሳሳት ያጥራቸዋል::
"አንድ ሻማ ከማብራት ጨለማውን እየረገሙ መኖርን"ይመርጣሉ
በዚያ ላይ መንፈስንና ሞራልን ዘንግተናል:: ስለዚህ እንደፈለግን እንሰርቃለን እንደፈለግን እንራመዳለን:: ለሀገር ያለብንን ሰዋዊ ግዴታ የምናስተውልበት ህሊናችን ሟልጯል::
ለውጡን ከራሳችን እንጀምር::እዚህ ላይ አንድ ጥቅስ ላስቀምጥ
"Education without morals would only make you a clever devil" C.S Lewis

No comments:

Post a Comment