Search This Blog

Saturday, August 20, 2011

36 ብር ቅጣት!!!!???




ዛሬ ወደ መብራት ሐይል ክፍያ ጥሎኝ ሄጀ ነበር:: ስደርስ ክፍያው መፈፀም የነበረበት ከ 6-10 መሆኑን ተጨማሪም 3 ቀናት ተሰጥተው የመጨረሻ ቀን በ 13 እንደነበር እናም እንደምቀጣ ተነገረኝ:: ያሳሳተኝን ሰው ወቅቼ ለመክፈል ተዘጋጀሁ:: ዋጋውን ስጠይቅ 36 ብር ነው:: ክው እና ክውክው አልኩ:: 36 ብር የመክፈያ ቀን ስላለፈ?
የሳኣት አጠቃቀም ላይ ከባድ ችግር ያለብን እኛ አንቀጣ ማለቴ አይደለም:: ከበድ ያለ ቅጣት መጣሉም ሰው እንዝላል እንዳይሆን ያረግ ይሆናል:: ግን 36 ብር? ከመናገር ወደ ኋላ ማለት አልቻልኩም:: ፊቴን ኮስኩሼ ድምፄን ግን አለስልሼ አስከፋይዋን እንዴት 36 ብር ብዬ ጠየኩ:: "እኛ እኮ የተቀመጥነው ለመስራት ነው.......ከ 8 ቀን በላይ እንዴት መታገስ ይቻላል?" አለችኝ:: ምክንያቷ አሳማኝ እንደሆነ ነገር ግን የብሩ መጠን እጅግ ከፍ እንዳለ ተናግሪ እንደሚከተለው ፎገርኩ
"ክፍያ ያሳለፈ 36 ብር ከተቀጣ ህገ-መንግስቱን የተላለፈ እንዴት ሊቀጣ ነው?"
ሴትዮዋ ቀና ብላ ገርምማኝ "እሱን እነሱ ያውቃሉ::" አለችኝ:: እነሱ ማናቸው???
36 ብር? የህይወት ሩጫ ከ 36 ከፍሎት በድህነት እየተቆላ ለሚኖር ህዝብ 36 ብር ቅጣት?? ለምሳሌ በወር ከ 6 ብር በላይ የማይከፍሉና በዚህ ወር ሰው ታሞባቸው የሆስፒታል ቀዝቃዛና ሸታታ ወለል ላይ ተኝተው ሲያስታምሙ መድሐኒት መግዣ አጥተውም ሲቃዡ ክፍያ ያለፋቸው "እመት" ቢኖሩ 36 ብር ቢቀጡ ምን ይውጣቸዋል????
መብራት ሀይል ሆይ ቅጣቱ በየቤታችን ከሚደርሰውና ሲያሻው ከሚቆራረጠው የሀይል አቅርቦት ይልቅ አላየለም ወይ?
(በነገራችን ላይ ቅጣቱን አልከፈልኩም......በከምፒውተር ስኅተት(ምስኪኑ ከምፒውተር!!)የባለፈው ወር ሂሳብ በድጋሜ ካሁኑ ጋር ተድርቡ በመምጣቱ ምህረት ተደርጎልኛል)
//---//
ክብር ከዘላለም ቅጣት ለገላገለን ለክርስቶስ ኢየሱስ!!
ሐምሌ 14 2003 ዓ.ም
ከሳር ቤት 6 ኪሎ እስክደርስ ብሶቱ ልቤ ላይ ተሳለ::

Saturday, August 13, 2011

ነገረ-ሊሾ& ነገረ ህንጻ

የ አዳም ረታን " ያመጣል መንገድ ይወስዳል መንገድ"የተሰኘ ልብለድ እያነበብኩ ነው:: አዳም እዚህም  እዚያም አፈርን ያነሳሳል:: ህይወታችን ከ አፈር ጋር የተቆራኜ እንደሆነ በ ትዕምርቶች (symbols)ይጠቁማል:: "ከአፈር ነህ ወደ አፈር ትመለሳለህ" የሚለውን እውነት ያንፀባርቃል::
እውነት ነው የዕለት ከለት ኑሯችን ከ አፈር ጋር ያገናኘናል( በተለይ ከ አፈር መንገድ እና ከአፈር ቤቶች ያልተላቀቅነዎችን አፍሪካውያንን:: ብዞዎቻችን  አፍሪካውያን በመልክ እንኳን ወደ አፈር እንጠጋለን:: ስማችን እንኳን ሳይቀር አፍሪካ( አፈር ኢካ--አፈር ነህ ማለት ነው በትግረኛ) ነው:: እናም ይኼ በየቦታው ያለ አፈር አፈርነታችንን እያስታወሰን አምላካችንን እንድናስብ የህየወትን ፍጻሜን ሞትንም አንዳንዘነጋ ያደርገናል:: ግን ደግሞ ጎድቶናል:: ከንቱ እንደሚሆን ማንንነት ብቻ እንድንመላለስ አበረታቶናል:: ከ አፈር በላይ' ከሞት በላይ መሆናችንን አምነን ከፍ ብለን እንዳንኖር የአፈሩ ሽታ አደንዝዞናል::
ግን ከ አፈር የተላቀቁት ወለላቸውን ሊሾ ወይ ሴራሚክስ 'ህንፃቸውን ድንጋይ ወም ብሎኬት የሚያደርጉት ምዕራብውያንና ሌሎችስ? መጀመሪያውኑ ከ አፈር መላቀቅ ወደ ድንጋይ 'ወደ ብሎኬት 'ወደ ሴራሚክስ 'እና ወደ አስፋልት መሸጋገር ለምን ፈለጉ? ለስልጣኔ የሚለው ጥሩ የሚመስል ምክንያት ይቆዬን:: እኔ አንድ ነገር ይታየኛል:: ሞትን መፍራትቸው& እግዚአብሄርንም መናቃቸው:: ወለላቸው አፈር 'ቤታቸው አፈር 'መንገዳቸው አፈር ቢሆን ኖሮ አፈርነታቸውን በየለቱ አምላካቸውን ደግሞ ቢያንስ በየሰለስቱ ያስቡ ነበር:: ግን በሞት ፍርሃታቸው  በእግዚአብሄር ሽሽታቸው ምክንያት ወለላቸውን በሲሚንቶ ይሸፍናሉ:: ህንጻዎቻቻው በድንጋይ-ብሎኬት ይሰራሉ:: ነገሩ ተሸወዱ እንጂ ከሰማይ በታች ከ አየሩ በስተቀር አፈር ከመሆን የሚቀር ነገር የለም:: ድንጋዩም ሊሾውም የአፈር ዘር ነው:: ግን ለጊዜው ካፈር ይደበቃሉ(ላይተርፉ) ከ እግዚአብሄር ይሸሻሉ(ላያተርፉ)::
ታዲያ ይቺ አፈርን መጥላትና እግዚአብሄርን መሸሽ ወደ አፈር-ኢካም(አፈር ኢካ-አፈር ነህ)እየተዛመተች ነው:: ከአፈር ከተላቀቁ እናም አፈርነታቸውን ረስተው በትዕቢት ከታነቁ ወገኖች(ለምሳሌ ምዕራባውያን) አልተማርንም:: በርግጥ የሞት ቤት የሆነው አፈር ባሰቡት ቁጥር ልብን የሚያርድ እናም የሚያስበረግግ መሆኑ አልጠፋኝም::

ግን እውነተኛ እውነት እውነተኛም ተስፋ አለ:: ክርስቶስ እየሱስ ከ አፈር ብቻ ከመሆን አላቆ ነፍሳችንን ከሞት ነጥቆ በጉያው ሸጉጦ መንፈሳችንን በሰማያት ስፍራ ከራሱ ጋራ ሊያስቀምጥ ወዷል::ክብር ለስሙ ይሁን!!
ሐምሌ 30 '2003 ዓ.ም ረፋድ ላይ
6 ኪሎ ካምፓስ NCR  ህንጻ